image
image
image
image
image

በጤናው ዘርፍ ያለውን አገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል የእንጠያየቅ መድረክ ጉልህ ሚና እንዳለው ተገለፀ

ጥር 1, 2018
በልደታ ክፍለ ከተማ ጤና ጽ/ቤት ባዘጋጀው የእንጠያየቅ መድረክ ላይ በጤና አገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ ከተገለልጋይና ከአገልግሎት ሰጪ ተወካዮች ጋር የፊት ለፊት ውይይት አካሄደ። በመድረኩም በበሽታ መከላከል፣ በጤና መድህን ሽፋን፣ በቤት ለቤት አገልግሎት ቅድመ መከላከል፣ በእናቶችና ህፃናት ጤና እንዲሁም በአጠቃላይ የጤና ሽፋን ዙሪያ የተሰሩ ስራዎች ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጓል። የልደታ ክፍለ ከተማ ጤና ጽ/ቤት ሃላፊ የሆኑት አቶ መስፍን በየነ እንዳሉት መድረኩ ተገልጋዩ ማህበረሰብ በተለያዩ ጊዜያት በጤና አገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ የሚያነሳቸውን ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እንዲያገኝ እድል የሚሰጥ ከመሆኑ ባሻገር በአገልግሎት ሰጪ ተቋማትና በህብረተሰቡ መካከል መተማመንን በመፍጠር በጋራ ለመስራት የሚያስችል መሆኑ ገልጸዋል። በዕለቱም የክፍለ ከተማና የወረዳ አመራሮች፣ የጤና ተቋማት የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፎ አድርገዋል።

መልዕክትዎን ይላኩ